የጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ቤተ–መፅሀፍና ዶክመንቴሽን
የጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ቤተ-መፅሀፍቶች በዋናነት ሁለት ያሉት ሲሆን አገልግሎቱም በተደራጀ መልኩ በባለሙያ የሚመራ ነው፡፡
የስራ ዘርፍ ሃላፊ/ተጠሪ /፡- ብርቱካን ስማቸው , email :- lib@gcte.edu.et
በስራ ዘርፉ ያሉ ክፍሎች
- ካታሎግ እና ክላስፊኬሽን
- ሰርኩሌሽን
- ባይንዲግ እና ሌሎችም
- የስራ ዘርፉ የሰው ሃይል በሁለቱም ቤተ-መፅሃፍት
የሰው ሃይል ብዛት
ሴት ወንድ
7 1
የትምህርት ደረጃ
- 1 ሴት ማስተር
- 2 ሴት ዲፕሎማ
- 4 ሴት ዲግሪ፣ 1 ወንድ ዲግሪ
የስራ ዘርፉ ዋና ዋና ተግባራት
- መጽሃፍትና ላሎች የቤተ-መጽሃፍት ንብረቶች በአግባቡ መያዝ፣ በየአመቱ የንብረት ቆጠራ ማካሄድ፣
- የመጽሃፍትን ደህንነት ለመጠበቅ ልዩልዩ የአሰራር ስርአት መዘርጋት፣
- የቤተመጽሀፍት ክበብ በማቋቋም ክበቡ እገዛ እንዲደርግና አባላት ከክበቡ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ፣
- የመጽሀፍትን እድሜ ለማራዘም የመጽሀፍት ጥገና/ድጎሳ ተደርጓል፣ ጋዜጦች መደጎስ፣
- የንባብ ባህልን ለማዳበር የሚያግዙ ልዩልዩ ስልቶች ቀይሶ ተግባራዊ ማድረግ፣
- የአንባብን/የተገልጋዮች መረጃ በዘመናዊ መልክ መያዝ፣ ለባለድርሻ አካላት በየጊዜው በተለያዩ መንገዶች መግለጽ፣ አዳዲስ ዕትሞችን ለተጠቃሚዋች ማሳወቅ፣
- ተፈላጊ መጽሃፍት በወቅቱ እንዲቀርቡ ማድረግ፣ አዳዲስ መፅሃፍትን ካርድ ካታሎግ ማዘጋጀት፣ ለተጠቃሚዋች ተገቢውን መረጃ መስጠት፣
- ልዩልዩ ጋዜጦችና መጽሄቶች በወቅቱ ለአንባብያን እንዲቀርቡ ማድረግ፣
- የአንባብያንን የንባብ ጊዜ በሚገባ ማክበር፣
ያሉት ፋሲሊቲዋች
- በሁለት ቤተመጽሃፍት 11,981 መፅሃፍቶች ክምችት መኖሩ፣
000-099 Computer science, information & general works -1,110
100-199 Philosophy & psychology ——————————499
200-299 Religion —————————————————–53
300 -399Social sciences ——————————————-2,016
400-499 Language ————————————————987
500 -599Science ————————————————–3,007
600 -699Technology ——————————————–310
700 -799Arts & recreation———————————–320
800-899 Literature ——————————————-2,944
900-999 History & geography—————————-735
አጠቃላይ ድምር——————————11,981
የቤተመጽሃፍቱ የ2011ዓ.ም የሁኔታዎች ትንተና (SWOT)
- ጥንካሬ (Strength)
- በቤተ-መፃህፍቱ ውስጥ ያለው በጥንካሬ የምንይዘው
- ሀላፊዎች ለቤተ-መፃህፍቱ ልዩ ትኩረት በመስጠት ድጋፍ ማድረጋቸው፤
- መጽሀፎችና መጽሄቶች ጋዜጦች በአግባቡ የተደራጁ መሆናቸው
- ሰራተኞች ከሞላ ጎደል ስለ ቤተ-መፃህፍት አጠቃቀምና አሰራር ግንዛቤ ያላቸው መሆኑ ፤
- ለመጽሀፍ ጥገና የሚያገለግሉ ማቴሪያሎች በወቅቱ እየቀረበ መሆኑ፤
- ለቤተ-መፃህፍቱ የሚያገለግሉ የተለያዩ ሸልፎች በበቂ ሁኔታ ያለ መሆኑ፤
- በተለይ ትልቁ ቤተ-መፃህፍ ለአንባቢ አመች የሆነ መሆኑ፤
- የጽህፈት መሳሪያዎች በወቅቱ እየቀረቡ መሆናቸው፤
- ለብዙ ዓመታት ያልተቆጠሩ የቤተ-መፃህፍት ንብረቶችና መፅሀፎች በ2011 ዓ/ም ቆጠራ መደረጉ
- ድክመት (Weakness) የምንላቸው
- መጽሀፎች መጽሄቶችን እና ጋዜጦች ወደ አዲቪዘዋል ሲሰተም አለመቀየር፤
- አብዛኛው የቤተ-መፃህፍት ሰራተኞች የኮምፒተር እውቀት ዝቅተኛ መሆን፤
- አንባቢዎች ተጠቅመው ሲወጡ የፍተሻ አገልሎት ደካማ መሆን
- መልካም አጋጣሚ (Opporatanity)
- የኮሌጁ ሀላፊዎች ለቤተ-መፃህፍቱ ጠንካራን ልዩ ድጋፍ ማድረጋቸው ፤
- የኮምፒተር አቅርቦት እየተሻሻለ መምጣቱ ፤
- ከነበረው አስራር በመውጣት ሰራተኞች በአዲስ እንዲደራጁ መደረጉ ፤
- በሰራተኞች መካከል ተግባብቶ መስራት፤
- የቤተ-መፃህፍት መስኮቶች በፍርግርግ የተሰራ በመሆኑ ከስርቆት ነፃ መሆኑ፤
- ለተማሪዎች የኢንተርኔት አገልግሎት ለመስጠት ዕቅድ መያዝ
- ማየት ለተሳናቸው ተማሪዎች አገልግሎት የሚውል ኮምፒተሮችና ሶፍትዌር እንዲሞላ መደረጉ
- ስጋት (Threat)
- ከፍተኛ የሰው ሀይል ችግር ስላለ የአንባቢያን ፍላጎቶች ለማሟላት አለመቻል የስራ ጥራት ያጎድላል፡፡
- በጀት በወቅቱ ላይለቀቅ ይችላል፤
- ይገዛሉ ተብሎ በእቅድ የተያዙ መጽሀፎች ከአንባቢያን ቁጥር ጋር ባይመጣጠኑ፤
- ንብረቱን ለመቆጣጠር ያመች ዘንድ የፍተሻ ሰራተኛ አለመኖር፤
- ለተማሪዎች የኢንተርኔት አገልግሎት ለመስጠት ዕቅድ ቢያዝም ያለው የተማሪና የሰራተኛ መጠን አለመጣጣም እና ያረጁ ኮምፒተሮች በመሆናቸው አገልግሎት ለመሰጠት መቸገር፤
- የእቅድ አለማና ግብ
- የማንኛውም ቤተመጽሀፍትና ዶክመንቴሽ አገልግሎት ዋና አላማ የተቋሙን ት/ትና አላማ ከግብ ለማድረስ ለተማሪዎች ለመ/ራንና ለአስተዳደር ሰራተኞች አስፈላጊውን መፅሀፍት በማሟላት የኮሌጁን በማህራዊና በሶሻል ሚዲያ የዳበረና የበለፀገ ተማሪዎች ከአሁኑ ማግኘት ያለባቸው እውቀት እንዲያገኙ ቤተ-መፃህፍቱ የድርሻውን ይወጣል፡፡
- በተቋሙ ለሚገኙ መ/ራን የአስተዳደር ሰራተኞች እና ተማሪዎች አስፈላጊውን ድጋፍ በመስጠት በንባብና በጥራትና ምርምር ግላዊ ዕውቀታቸውን በማዳበርና ተማሪዎች ብቁና አገር ተረካቢ ትውልድ ሆነው እንዲወጡ ልዩ እገዛ የሚደረግበት ቦታ ነው፡፡
- ተማሪዎች ቤተ-መፃህፍት ቢውሉ ከአዲሱ ካሪክለም ጋር በተቀረፁት መፅሀፎች ተጠቅመው ራሳቸው ውጤታማ እንዲያደርጉ እና ሁሉም ተማሪዎች የተሻለ ውጤትና ደረጃ እንዲኖራቸው ማድረግ ነው፡፡
- ዘመናዊነት የተላበሰ ቤተ-መፃህፍት ማደራጀት፤
- በቤተ-መፃህፈቱ ዙሪያ ወቅታዊ ችግሮች የመፅሀፍት እጥረት የመሳሰሉትን መፍታት፤
- ለተጠቃሚዎች ቀልጣፋና ትህትና ባለው መልኩ ማስተናገድ፤
- የተሻለ አሰራር ካላቸው የቤተ-መፃህፍት የአሰራር ልምድ ልውውጥ ማድረግ፤
- ያረጁና የተገነጠሉ መጽሀፍትን መጠገን፤
- የተናጠልና የጋራ ተግባራትን መፈፀም
- ቤተ-መፃህፍቱ ሊሰጥ ከነበረው 2012ዓ/ም የተሻለ ስራ መስራት ፤
- የአንባቢያን ፍላጎት ለማጎልበት እና ለማዳበር አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ፤
- ወደ ቤተ-መፃህፍት ለሚገቡ አዳዲስ መፅሀፍት የካታሎግና የመለያ ቁጥር ኪስ በማዘጋጀት ለአገልግሎት ዝግጁ ማድረግ፤
- ቸክሊስት በማዘጋጀት ስራዎችን መቆጣጠር፤
- የአንባቢያን ብዛትና የመፅሀፍት ክምችት ብዛት እስታስቲካዊ መረጃ መያዝና ለሚመለከተው ማስተላለፍ፤
- ካርድ ካታሎግ ለሌላቸው መፅፍት ማዘጋጀት፤
- የተቋሙ ንብረት በአግባቡ መጠቀም
- አመታዊ ንብረት ቆጠራ እንዲካሄድ ማድረግ፤
የስራ ዘርፉ የ2012ዓ.ም አንኳር ውጤቶች
- በቤተመጽኃፉ ባለሙያዎች የዕርስ በዕርስ ስልጠና መካhሄዱ
- ከአጋር ኮሌጆች ጋር የ ልምድ ልውውጥ መደረጉ
- በፕሮፌሰር ሞገሴ አሸናፊ በስጦታ በርካታ ዘመናዊ ስነ-ሕይወት መሰረታዊያን መጽሃፍት ተበርክተዋል
የ2012ዓ.ም ክትትልና ግምገማ ቁልፍ የውጤት አመልካቾች
ተ.ቁ | ተግባራት | መለኪያ | የ2011ዓ.ም አፈጻጸም | የ2012ዓ.ም ዕቅድ | የ2012ዓ.ም ዕቅድ በሩብ ዓመት | ምርመራ | ||||
1ኛ ሩብ ዓመት | 2ኛ ሩብ ዓመት | 3ኛ ሩብ ዓመት | 4ኛ ሩብ ዓመት | |||||||
1 |
ስራ አመራር፣አደረጃጀት፣ውሳኔ አሰጣጥና አተገባበር ሥርአት ተሸሽሏል |
|||||||||
1.2 | የስራ ዘርፉ እና በስራዘርፉ ስር ያሉ አደረጃጀቶች የ2011ዓ.ም አፈጻጸም ግምገማ/የሁኔታ ትንተና በማድረግ እቅድ አዘጋጅተዋል፣ በእቅድ ተመርተዋል | በ% |
80% |
80% |
25% |
25% |
25% |
|||
1.3 | ከ2012ዓ.ም ዕቅድን መሰረት በማድረግ ለክትትልና ድጋፍ/ስራን ቆጥሮ ለመስጠትና ለመቀበል የሚያስችል ቼክሊስት ተዘጋጅቷል | በ% |
80% |
90% |
30% |
35% |
20% |
|||
1.4 | በልዩልዩ የአቅም ግንባታ ሰራተኞች | በቁጥር | 0 | 8 | ||||||
1.5 | በስራ ዘርፉ ግምገማዊ ውይይት/እቅድ
አፈጻጸም፣ በውጤት ተኮር አፈጻጸም/ የተሳተፉ መምህራን/ሰራተኞች |
በቁጥር | 8 | 8 | 8 | 8 | 8 | |||
1.6 | ሁሉም የሩብ አመት እና በየጊዜው የሚጠየቁ ሪፖርቶች በጥራት ተዘጋጅተው በወቅቱ ተልከዋል | በቁጥር | 4 | 4 | 1 | 1 | 1 | |||
1.7 | የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል ተገልጋችን እርካታ ለማሳደግ የተካሄዱ የሀሳብ መስጫ ሳጥን ማስቀመጥ | በቁጥር | 1 | 1 | 1 | 1 | 1 | |||
1.8 | የላብ ቶፕ ኮምፒተር ስርጭት/ ለመምህራን/ ሰራተኞች/ | በቁጥር | 0 | 1 | 0 | 0 | 0 | |||
1.10 | የኢንተርኔት/ዋይፋይ አገልግሎት/ ለመምህራን/ ሰራተኞች/ | በ% | 0 | 99% | 0 | 0 | 0 | |||
1.11 | በቤተመጽሀፍት አገልግሎት ያገኙ ተጠቃሚዎች | ወንድ | በቁጥር | 123,213 | 180,113 | 30,000 | 30,350 | 29,706 | ||
ሴት | በቁጥር | 114,926 | 140,928 | 32,800 | 32,320 | 20,328 |
የ2012ዓ.ም ክትትልና ግምገማ ቁልፍ የውጤት አመልካቾች
ተ.ቁ | ተግባራት | መለኪያ | የ2011ዓ.ም አፈጻጸም | የ2012ዓ.ም ዕቅድ | የ2012ዓ.ም ዕቅድ በሩብ ዓመት | ምርመራ | |||
1ኛ ሩብ ዓመት | 2ኛ ሩብ ዓመት | 3ኛ ሩብ ዓመት | 4ኛ ሩብ ዓመት | ||||||
1..12 | የተማሪዎችን ስነምግባር ለማሻሻል በተሰራው ስራ በዲሲፕሊን የተቀጡ ተማሪዎች | በቁጥር | 16 | 20 | 8 | 10 | 4 | ||
ግብ | |||||||||
2.1 | 1. ለነባርና አዲስ ተማሪዎች፣ ለመምህራንና ሰራተኞች እንዲሁም የቤተ-መፃህፍቱን አገልግሎት ለሚፈልጉ የውጭ ተጠቃሚዎች የንባብና የውሰት አገልግሎት መስጠት | በ% | 80% | 99% | 60% | 70% | 60% | ||
2.2 | 2. ወደ ኮሌጁ የሚገቡ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች ስለቤተ-መፃህፍት አጠቃቀም ኦሬንቴሽ በመስጠት በአግባቡ እንዲጠቀሙ ማድረግ፤ | በ% | 80% | 100% | 50% | 50% | 50% | ||
2.3 | 3. ሀገራዊና ወቅታዊ መረጃዎችን ተጠቃሚዎች በወቅቱ እንዲያገኙ ለማስቻል የጋዜጦችና መጽሔቶች አገልግሎት መስጠት፤ | በ% | 90% | 100% | 70% | 75% | 80% | ||
2.4 | 4. ስለቤተ-መፃህፍት ሙያ፣ አደረጃጀት እና አገልግሎት የስራ ጊዜን በማይነካ መልኩ የግንዛቤ ማሳደጊያ ስልጠና ለስራተኞች መስጠት፤ | በ% | 80% | 80% | 60% | 70% | 50% | ||
2.1.1 | መጽሔት፣ ጆርናሎች እንዲሁም ጋዜጦችና መጽሔቶች እንዲገዙ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ግዥው እንዲፈፀም ማድረግ፤ | በ% | 80% | 80% | 70% | 75% | 75% |
የ2012ዓ.ም ክትትልና ግምገማ ቁልፍ የውጤት አመልካቾች
ተ.ቁ | ተግባራት | መለኪያ | የ2011ዓ.ም አፈጻጸም | የ2012ዓ.ም ዕቅድ | የ2012ዓ.ም ዕቅድ በሩብ ዓመት | ምርመራ | |||
1ኛ ሩብ ዓመት | 2ኛ ሩብ ዓመት | 3ኛ ሩብ ዓመት | 4ኛ ሩብ ዓመት | ||||||
2.1.2 | ጥረዛና ድጎሳ የተደረገላቸው መጽሐፍት | በቁጥር | 500 | 600 | 200 | 150 | 200 | ||
2.1.3 | ወራሃዊ ወደ ቤተ-መፃህፍት የሚገቡ ጋዜጦችንና መፅሄቶች መረከብና መጠረዝ | በቁጥር | 1053 | 1053 | 500 | 250 | 400 | ||
3 | ንዑስ ተግባር | ||||||||
3.1 | ለቤተ-መፃህፍት አገልግሎት የሚውል የተለያዩ ቅፆን፣ ካርዳች እና የማዋሻ ፖኬቶችን ማሳተም | በ% | 60% | 60% | 0 | 0 | 0 | ||
3.2 | ኮፒያቸው ያነሱና ገፃቸው የተገነጠሉ መጽሀፍትን ፎቶ ኮፒ ማድረግ፤ | በ% | 60% | 70% | 50% | ||||
3.3 | ለቤተ-መጻህፍት አስፈላጊ የሆኑ እስታስቲካዊ መረጃዎችን መያዝ፤ | በቁጥር | 2 | 2 | 2 | 2 | 2 | ||
3.4 | በግዥም ሆነ በእርዳታ የገቡ መጽሐፍትን አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማጠናቀቅ ካታሎግና ክላስፊኬሽን ሰጥቶ ለአገልግሎት እንዲበቁ ማድረግ፤ | በ% | 88% | 88% | 50% | 60% | 50% | ||
3.5 | በየሩብ ዓመቱ መጨረሻ የቤተ-መፃህፍቱን የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ማቅረብ | በ% | 90% | 90% | 60% | 65% | 70% | ||
3.6 | በየሴሚስተሩ የተቀመሩ/ እንዲሰሩ የተደረጉ ተሞክሮዎች/ | በቁጥር | 3 | 5 | 0 | 0 | 0 | ||
3.7 | የመጽሐፍ ግዥ | በቁጥር | 98 | 140 | 0 | 0 | 4 |